የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ብልጽግና ፓርቲ “ቃልን በተግባር ለኢትዮጵያ ብልጽግና” በሚል መሪ ቃል ክልላዊ የአባላት ማጠቃለያ ኮንፍረንስ እያካሄደ ነው::

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የብልጽግና ፓርቲ አባላት ክልላዊ ማጠቃለያ ኮንፍረንስ “ቃልን በተግባር ለኢትዮጵያ ብልጽግና” በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ነው።

በኮንፍረንሱ ላይም ብልፅግና ፓርቲ ባለፉት አምስት ዓመት የምርጫ ዘመን የሁለት ዓመት ተኩል አፈጻጸም ፣ተግዳሮቶች እና የተገኙ ውጤቶች በዝርዝር ቀርቦ ውይይት ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

በኮንፍረንሱ ማጠቃለያ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻዲሊ ሀሰን፣የክልሉ ም/ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታሁን አብዲሳ፤ የክልሉ ም/ቤት አፈ-ጉባኤ ዶ/ር ተመስገን ዲሳሳ ፣የክልሉ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኢሳቅ አብዱልቃድር፣ የክልሉ ም/ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ወ/ሮ አለምነሽ ይባስን ጨምሮ የክልል የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ፣በየደረጃው የሚገኙ የብልጽግና ፓርቲ አባላት እየተሳተፉበት ይገኛል፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *