የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ የመንግስት ሰራተኛው በጋራ ሊቆም እንደሚገባ የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወ/ሮ አስካለች አልቦሮ ገለጹ

‎(አሶሳ፣ መስከረም 22/2018 ዓ/ም) የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም እውን ለማድረግ የመንግስት ሰራተኞች በጋራ መቆም እንደሚገባ የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወ/ሮ አስካለች አልቦሮ ገለጹ።

‎”‎የታደሰ ጂኦ-ስትራቴጂያዊ ቁመና፣ በሁሉም ኢትዮጵያውያን የጋራ ትጋት” በሚል ወቅታዊና ሀገራዊ ሰነድ ዙሪያ የውይይት መድረክ ተካሂዷል።

‎በመድረኩ የተገኙት ‎የክልሉ ምክር ቤት ቤት አፈ ጉባኤ ወ/ሮ አስካለች አልቦሮ እንደገለጹት ሀገራችን ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ያጋጥሟትን ውስጧዊና ውጫዊ ፈተናዎችን በመሻገር አመርቂ ውጤቶች እያስመዘገበች እንደሚገኝ ገልጸዋል።

‎‎የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅሞችን ለማስጠበቅ የመንግስት ሰራተኛው አንድነቱን ሊያማጠናከር ይገባል ብለዋል።

‎የክልሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ መለሰ በየነ “የታደሰ ጂኦ-ስትራቴጂያዊ ቁመና፣ በሁሉም ኢትዮጵያውያን የጋራ ትጋት!” የሚል ሰነድ ባቀረበቡት ወቅት እንደገለጹት መንግስት ሰራተኞች ዓለም አቀፋዊ ወቅታዊ ሁኔታዎች በአግባቡ መረዳት እንዳለበት ገልጸዋል።

‎‎ፈተናዎች ድሎችን እንድንቀናጅ በር እየከፈተ በመሆኑ መላው ኢትዮጵያዊያን አንድነታቸውን በፅኑ መሰረት ላይ ሊያቆሙ ይገባል ብለዋል።

‎‎ጠንካራ ሀገር ለመፍጠር ሲቪል ሰርቫንቱ የአገልጋይነት ስሜትን በመላበስ የተገልጋዮችን እርካታ ማሳደግ ተቀዳሚ አጀንዳው ማድረግ እንደሚጠበቅበትም ተናግረዋል።

‎‎ያለፉትን ኩስመና አጀንዳ በመዝጋት ወደ ሀገራዊ ዘላቂ ቁመና ለመሸጋገር የጋራ ርብርብ እንደሚጠይቅም አቶ መለሰ ገልጸዋል።

‎በመድረኩም የክልሉ መስተዳድር ምክር ቤት፣ የክልሉ ምክር ቤት፣ የክልሉ መንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ፣ የክልሉ ዋና ኦዲተር መ/ቤት፣ የታላቁ ህደሴ ግድብ ማስተባበሪያ ምክር ቤት ጽ/ቤት፣ የክልሉ ሳይንስ ቴክኖሎጂና ኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ኤጄንስ አመራሮችና ሰራተኞች ተገኝተዋል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *