በክልሉ 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በዓል በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ይገኛል

‎‎በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በዓል በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ይገኛል።

‎‎በዓሉም በክልል ደረጃ “ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለኅብረ ብሄራዊ አንድነት” በሚል መሪ ሃሳብ የክልል ሴክተር መስሪያ ቤት ሰራተኞች በፓናል ውይይት አክብረዋል።

‎‎የክልሉ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ አቶ መለሰ ኪዊ፣ በክልሉ የብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች በዓል መከበሩ ህገ መንግስቱ ያጎናፀፋቸው መብቶቻቸውን የሚያንፀባርቁበት ነው ብለዋል

‎‎ባለፉት ዓመታት የተከበሩት የብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች የጋራ አንድነት እና አብሮነታቸው በፅኑ መሰረት ላይ እንዲቆም አስተዋፅኦ ማድረጉን ተናግረዋል።

‎‎የዘንድሮው የብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች በዓል ለየት የሚያደርገው ሀገራችን በመፍጠንና በመፍጠር እሳቤ የተጀመሩ በርካታ ፕሮጀክቶች በተጠናቀቁበት ማግስት መሆኑ ልዩ እንደሚያደርግ ምክትል አፈ-ጉባኤው ገልጸዋል።

‎‎በክልሉ የማጠቃለያ መድረክ በካማሽ ዞን ካማሽ ከተማ ላይ ይከበራል ያሉት ምክትል አፈ ጉባኤው፣ ይህም በዞኑ ያሉትን እምቅ የተፈጥሮ ፀጋዎችን ለማስተዋወቅና ለማልማት ትልቅ አጋጣሚ መሆኑን ጠቁመዋል።

‎‎በአሶሳ ዩኒቨርሲት የፌደራልዝም መምህር ረዳት ፕሮፌሰር አዳሙ ጅባት እንደገለጹት፣ የተለያዩ ብሔሮች እና ብሔረሰቦች ባህሎችን በማክበር የማኅበራዊ ውህደትን በማጎልበት የጋራ መለዮዎችን እና ታሪካዊ እውነታዎችን በማካፈል ዘላቂ ሰላምን ለማጠናከር ያግዛል ብለዋል።

‎‎የእያንዳንዱ ብሔር መብት እና ክብር መከበሩ የሰብዓዊ መብቶች እና እኩልነት ተጠብቀው የተበታተኑ ማህበረሰቦች ድምጻቸውን የሚሰሙበት መድረክ እንደሚፈጥር ረዳት ፕሮፌሰሩ ገልጸዋል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *